አዲስ መጽሐፍ ጥቆማ " እስረኞቹ " እንዳለጌታ ከበደ ኢትዮጵያ ውስጥ ሃሳባቸውን በነጻነት በመግለጻቸው ብዙዎች ተገስጸዋል፣ በገንዘብ ተቀጥተዋል፤ ከደረጃቸው ዝቅ ተደርገዋል፤ ተሰደዋል፤ ታስረዋል፤ለሞት ተላልፈው ተሰጥተዋል። ደግሞም በየዘመናቱ የታሰሩ ከያኒዎች እና ጋዜጠኞች ብቻ ሳይሆኑ የታሰሩ ሃሳቦችም አሉ። ለጊዜው ወይም ለዘለቄታው የተቀመጡ። የታሰረው ወይም የሚታሰረው ግለሰብ ብቻ አይደለም፡፡ ግለሰቡ ሲያስበው የነበረው ሃሳብ ብቻም አይደለም፡፡ አሳሪውም ታሳሪ ነው፤ ብሎ ራሱን አሳስሮ የተገኘ . . .በነጻነት የተገለጸውን ሃሳብ ምን መዘዝ ያስከትልብኝ ይሆን? ብሎ በመሳቀቅ ዘመኑን የፈጀ . . . እና ይህ መጽሐፍ ስለእነዚህ እስረኛ ስለነበሩ ግለሰቦች፣ እስረኛ ስለሆኑ ሃሳቦች እና ይተርካል፣ እያሳቀም፣ እያሳቀቀም ፤ እያስለቀሰም ፣ እያጫወተም ፣ እያጨዋወተም. . . ን እና ን ያወጋል። 4.2K views18:45